Showing posts with label የጠቋር መንፈስ ጠባያትና አያያዝ. Show all posts
Showing posts with label የጠቋር መንፈስ ጠባያትና አያያዝ. Show all posts

Tuesday, May 10, 2016

የጠቋር መንፈስ ጠባያትና አያያዝ .

የጠቋር መንፈስ ጠባያትና አያያዝ .
የጠቋር መንፈስ ከሌሎች ክፉ መንፈሶች ሁሉ እጅግ በጣም ለየት የሚያደርገው ስዎችን ከአቅም በላይ በሆነ መንገድና ሁኔታ ውሰጥ በእጅጉ የሚፈትን አሮጌውን በአዲስ ለመተካት የሚያስችል የተለያዩ የጥቃት ሥልቶች ያሉትና በአንድ ጊዜ በርካታ የጥቃት ግንባሮችን በሰው ህይወት ላይ መክፈት የቻለ ወይም የሚችል አደገኛ መንፈስ መሆኑ ነው ፡፡ በህብረተሰቡ ውስጥ መንፈሳዊ መልአክ ጠባቂና ጸሎተኞ የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ይህንን ስም ተከትሎ የሚሄድ ማንኛውምንም ሌላ መንፈስ በመጫን ለራሱ የተሻለ ቦታ በመስጠት እልከኞ የመሆን ከፍተኛ አቅም ያለውና የመሪነት ስሜት የሚታይበት መንፈሰ ነው ፡፡
. .
መንፈሱ የህንን ሥያሜውን ያገኘው ለብዙ ዘመናት በኮከብ ቆጠራ ሲያሟርቱ በሚኖሩ ሰዎች አማካኝነት ነው ፡፡ የመጠሪያውንም ጠባይ ተከትሎ ጠቋር የሚለው ቃል አፍሪካዊ መንፈሰ መሆኑን ለማሳየት ነው ፡፡ በመሆኑም ሥያሜው ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥና ይዘት ያለው ሆኖ የሚንቀሳቀስ መንፈስ ነው ፡፡
. .
ከዚህ በተጨማሪም ሥራው የጠቆረ ህይወት የጨለማ ኑሮን የሚገልጥ የሚያመለክትና የሚያጎናጽፍ ነው ፡፡ ግብር ስጦታውና ሽልማቱ ጥቁር ቀለም ያለበት እንስሳም ይሁን አልባሳት የፍላጎቱ መለያ ነው ፡፡ በአብዛኛው ለማለት ይቻላል ጥቁር ቀለም የጠቋር ዋነኞ መገለጫ ነው ፡፡
. .
ጠቋር በግራ እጁ ለሚሰራ ሰው ግራውን በቀኝ ለሚሰራውን ሰው ደግሞ ቀኙን ይይዛል ፡፡ ሰው እንደ ልቡ ተንቀሳቅሶ እንዳይሠራ ዋናውን ሀይሉን ክንዱንና ሕሊናውን በሥውር ይቋጣጠራል ፡፡ ሴቷ አጋንንት ሻንቂት ስትባል ወንዱ ደግሞ ጠቋር ሻንቆ ይባላል ፡፡ መንፈሱ ስያሜውን ያገኘው በአውደ ነገሥት ውስጥና ቀደም ሲል ሌዋውያን አይሁዶች ኢትዮጵያ በመጡበት ወቅት ሲሆን በዚሁ ጊዜም ሁለት ዓይነት ደብተራዎች አብረው መጥተው ነበር ፡፡
. .
የመጀመሪያዎቹ ታቦተ ጽዮንን የሚያገለግሉ የምሥጋናና የአምልኮት እግዚአብሔር ደብተራዎች (መንፈሰሳዊ ሊቃውንት) ሰሆኑ ሁለተኞቹ ደግሞ ምትሀታዊውን ትምህርት ከአረማውያን የተማሩ ሌዋያን ማለትም የእስራኤል ነገዶች ነበሩ ፡፡ ሁለቱም አገራችን ከገቡ ጊዜ ጀምሮ ሰፋ ያለ ቦታ ከማግኘታቸው ጋር ተያይዞ ሁለተኛው ወገን በቀጥታ የክፉው መንፈስ አካል ሆኖ በአውደ ነገሥቱ ምሪት ውስጥ ጠቋር የምለውን ስያሜ አገኘ ፡፡
. .
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲህ ዓይነቱ መንፈስ በገዢነት ላይ ሆኖ ከላይ እንደቆየ የሚያሳየን በዮሐንስ ወንጌል ፰ : ፴፱ ላይ የአብርሃም ዘር ነን የሚሉትን ተቆጣጥሮአቸው ነበር ጌታ ኢየሱስም ለመንፈሳዊ በረከት ተዘጋጁ ሲላቸው እኞ የቃል ኪዳን ተስፋና የአብርሃም ልጆች ነን ፡፡ እኞ ቀደም ሲል አምልኮት ራእይ ተስፋና የተሻለ እድል ከነበራቸው ዘሮች ውስጥ ነን እያሉ ይመጻደቁ ነበር ፡፡
. .
በቀደሙት አባቶች አምልኮት እየተኩራሩና እየተመኩ አስተሳሰባቸው ተግባራቸው ግን ተግባር የሌለው የወግ አምልኮትን መንገድን የተከተለ ነበር ፡፡ በቀደመው በአብርሀም ስም ሰማያዊ ተስፋን የሚያገኙ መሥሏቸው ኑሮአቸውን ግብዝነት በተመላ ፈሪሳውያንነት ይመሩ ነበር ፡፡
. .
በዮሐንስ ወንጌል ፰ : ፴፱
" መልሰውም። አባታችንስ አብርሃም ነው አሉት። ኢየሱስም። የአብሃም ልጆች ብትሆኑ የአብርሃምን ሥራ ባደረጋችሁ ነበር ፡፡ ነገር ግን አሁን ከእግዚእብሔር የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ፤ አብርሃም እንዲህ አላደረገም። እናንተ የአባታችሁን ሥራ ታደርጋላችሁ አላቸው። እኛስ ከዝሙት አልተወለድንም አንድ አባት አለን እርሱም እግዚአብሔር ነው አሉት፡፡ ኢየሱስም አላቸው። እግዚአብሔርስ አባታችሁ ከሆነ በወደዳችሁኝ ነበር፤ እኔ ከእግዚአብሔር ወጥቼ መጥቻለሁና፤ እርሱ ላከኝ እንጂ ከራሴ አልመጣሁምና ። ንግግሬን የማታስተውሉ ስለ ምንድር ነው? ቃሌን ልትሰሙ ስለማትችሉ ነው።እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ ፡፡" አላቸው ዲያብሎስ አባት ሊሆን የሚችልበት መንገድና አጋጣሚ በጣም ሰፊ ነው ፡፡ ከዚህ አንጻር ጠቋር የሚባለው መንፈስ ይህንኑ መንገድ ያጠናክራል ፡፡
. .
የፈሪሳውያን መንፈስና የጠቋር ሥልት በብዙ መንገድ ተመሳሳይነት ያለው ሲሆን የሁለቱም መግለጫ በማስመሰል ዘመንና ጌዜን ጨርሶ ከእግዚአብሔር ክብር መለየት ነው ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ሲነግረን
. .
"ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ለሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፥ እንዲህ ሲል። ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ መቅደስ ወጡ፥ አንዱ ፈሪሳዊ ሁለተኛውም ቀራጭ። ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ። ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን ። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር ። እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል።"
. የሉቃስ ወንጌል ፲፰ : ፱
በማለት የሚገልጸው ቃል ክፉ መንፈስ በሰዎች ላይ ሲያድር እንዲህ ዓይነት የውስጥ ትዕቢት በማሳደር ፈረሐ እግዚአብሔር በማራቅ እምነትን የሚፈትን መሆኑንን ከፊሪሳዊው የጸሎት ልምድ መገንዘብ እንችላለን ፡፡ በመሆኑም ጠቋር በመንፈሳዊ ሥፍራና በጸሎት ወቅት በትቢት ሰዎችን ሊያስትና አቅጣጫቸውን ሊያስለውጥ ይችላል ፡፡ በአገራችን ልማዳዊ አነጋገር ጠቋር ዳዊት ደጋሚ አሸዋ ቃሚ ቅጠል ለቃሚ የባላል ፡፡ እናቶች በዚህ መንፈስ በጣም ተታለዋል ፡፡ መንፈስ ውስጣቸው እያለ አብረው ይመነኩሳሉ < የእኔ እኮ...ዳዊት ደጋሚ ነው ! እንዲህ ቀላል አይደለም ቤተክርስቲያን ሳሚ ገዳማዊ መነኩሴ ነው ...ወዘተ እያሉ በስፋት እንዲቀበሉት የሚደርጋቸው ሲሆን አውደ ነገሥቱም ይህንን መንፈስ ያጠናክረዋል ፡፡
. .
. .
. የጠቋር መንፈስ ሥልቶች .
ይህ የጠቋር መንፈስ ከፍተኛ የማስገደድ ኃይል ስላለው ራሱን ትልቅ አድርጎ በማሳየት ሌሎች በግድ በትልቅነት እንዲቀበሉት ያደርጋል ፡፡
. .
• በሕልም በማስፈራራት
• ያሳየውን ራእይ በሚቀጥለው ቀን ተግባራዊ በማድረግ
• በሰውነት ውስጥ የተለያዩ ምልክቶች በመስጠት ነው ፡፡
. .
ጠቋር ሰዎችን በቀላሉ ለመያዝ የሚከተለው ሥልት ከሌሎች በላቀ ሁኔታ የተለያየና የበለጠ ነው ፡፡ከእነዚም ውስጥ በገባበት አጭር ጊዜ ውስጥ በአስገዳጅነት ከፍተኛ ሀይልን ተጠቅሞ በፍጥነት ልቡናን ሰውሮ ሕሊናን በማስጨነቅ ወደፈለገው አቅጣጫና በሚፈልገው መንገድ መምራት መቻሉ አንድ ነው ፡፡ ይህን ክፉ መንፈስ ብዙ አባቶችና እናቶች ለምደውታል ፡፡ ልምምድም በባሕር ውስጥ ካለው መሸነፍ ጋር የያይዞ ለአምልኮት ከሚሰጡት ቦታና በጸሎት ከሚቃወሙት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ደካማነት የተነሳ በቀላሉ ተቀብለውት እንዲኖሩ ያደርጋል ፡፡
. .
ጠቋር ከሕቡዓን (ከተሰወሩ) ቅዱስ ጋር ያገናኛል በማለት የመናፍስቱ ሹክሹክታ እንደዚ ቅዱሳን ድምፅ ምናባዊ ውልብታውን ደግሞ እንደ ፃድቃን ብርሃናዊ ገጽ በመቁጠር ለማሳመን የሚሞክር መንፈስ ነው ፡፡
በባሕርይ ውስጥ አባት ሆኖ የመቀመጥ የመያዝ ጠባዩ በሥፋት የታወቀ ነው ፡፡ ብዙዎች ጠቋርን መንፈሳዊ ነው! ምንም ጉዳት አያመጣም እንዲያውም ጠባቂ ረዳትና አጋዥ ነው ይሉታል ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ራእይን ይገልጣል ተብሎ የተለያዩ መሻቶችን የሚጠይቅና ባመኑትና በሰገዱለት ዘንድ የሚገበርለት መንፈስ ነው ፡፡
. .
. ጠቋር በጸሎት ሥፍራ የጸሎቱን ባሕርይ በዝማሬ ቦታ የዝማሬውን ባሕርይ ወዘተ ... ይከተላል ፡፡ መንፈሱ በጣም ጥንቃቄ የሚያደርገው በቅዱስ ቁርባን አምልኮት ላይ ብቻ ነው፡፡ በዚህ በኩል የሚመጣበትን የእግዚአብሔር መንፈሰ ጨርሶ ሊቋቋመው ስለማይችል ሰዎች ወደ ቅዱስ ቁርባንና ወደ እግዚአብሔር አምልኮተ እንዳይገቡ የመጀመሪያውን የመዘግየትና የመጎተት ውጊያ ይከፍታል ፡፡ ኑሮአቸውን የተሟላና የተሳካ እንዳይሆን አስሮ በመያዝ በእግዚአብሔር አምላክ እንዲማረሩ ያደርጋል ፡፡ በቤተሰብ ምሥረታ ውስጥም ገብቶ በልጆች አእምሮና ሕሊና ውስጥ አፍዝ አደንግዝ ለመሆን ጊዜ አይፈጅበትም ፡፡ ምክንያቱም አባት ተብሏልና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "እናንተ ከአባታቸው ከዲያብሎስ ናችሁ " ተብሏል ፡፡ ከላይ የሚነሳ ወንዝ ወደታች ለመውረድ ምን ያስቸግረዋል ? ጠቋር ከላይ ያለውን አጥብቆ ያዘ ማለት ታች ያለውን መቆጣጠር ይችላል ፡፡
. .
ጠቋር ሥልታዊ መንፈስ በመሆኑ ወደ ሰውነት ለገብ ሌሎች መንፈሶች የአሥራር ሥልቱን ያስተምራል ፡፡ ወደ እግዚአብሔር ቤት ወደ ጸሎተና ጸበል ሥፍራ ሰንሄድ ውጭ ተለይቶ የሚጠብቁንን መንፈሶች ሥልታቸውን ለውጠው ከጸሎትና ከጸበል መልስ ወደ ሰውነት ውስጥ በመግባት በልብ ውስጥ የነበረውን ሠላምና ጤና ማወክ እንዲጀምሩ ያበረታታል ፡፡
ሌሎች መንፈሶች እንዲደበቁ ተራ በተራ እንዲጨው ጊዜ እንዲያባክኑና ያስከተሉት ችግር እንዲባባስ ከማድረጉም በላይ የጠቋር መንፈስ ቶሎ እዳይያዝ በዋላ የገባውን መንፈስ አጋፍጦ በመስጠት ራሱን ደብቆ መንፈሶቹ ከወጡ በዋላ ተመልሰው እንዲገቡ ደጋግሞ በሌላ ዓይነት አቀራረብ እንዲናገሩና እንዲጮዉ በማድረግ ዘዴውን ይቀይሳል ፡፡
" የአማልክት አምላክ፥ የነገሥታትም ጌታ፥ ምሥጢርም ገላጭ ነው። "
( ትንቢተ ዳንኤል ፪ : ፵፯)
ጠቋርን በሁለት መንገድ እናገኘዋለን
1'ወደ አውደ ነገስት የኮከብ ቆጠራ ውስጥ ስንገባ
2'ጊዜና ዘመኔን ፍታልኝ ብለን ወደ ጠንቋይ ቃልቻው አስማተኛውና መተተኞው ዘንድ ስንሄድ ነው ፡፡
. .
. 'ከጠቋር የረቀቀ ምሥጢራዊ የጥቃት ዘዴዎች መካከል .
. .
• ሰዎችን በፍጥነት የመልመድ ጠባዩና በከፍተኛ ደረጃ ተመሳስሎ የመኖርና የማድፈጥ ችሎታው
• አንዳንዴ የምታያቸውን ራእዮች እውነተኞ ለማስመሰል ሰፋ ያለ ጊዜና መንገድ በሕይወትህ ውሰጥ መምራት መቻሉ
• ባሕርይህን የመምሰል ጠባዩ የተዋጣለት መሆኑ
'ለጸሎት ስትዘጋጅና ስትጸልይ የሚያመጣው ፈተና '
• የትግሉ ሥልት በኑሮህ ውስጥ ያሉትን ጎዶሎዎች በሙሉ በልብህ ላይ ይጽፍልሃል በዚህም ሃሳብህ ይከፈልና ጸሎትህን ያሰናክላል
• ባለፋ ጉዳዮች ላይ እንድትጨነቅና ምነው እንዲህ ባረኩት ኖሮ ብለህ እንድታስብ በጸልሎትህ ሰዓት ሃሳብ ያመጣልሃል
• ወደፊት የምትሠራቸውን ሥራዎች ከፊትህ ያመጣብህና እንከኖችን በመደርደር በሀሳብ እንድትዋጥ ያደርግሃል በዚህ ጊዜ ፍንጭ ሳይሰጥህና የማንነቱ ጠባይ ሳይታወቅ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ውስጥ ባሉት ርምጃዎች ሁሉ ብዙውን መንገድ አብሮህ ስለሚጓዝ አታውቅውም ፡፡ ምክንያቱም ማንነቱና ምንነቱ በአንተ ባሕርይ ውስጥ የተደበቀ ነው ፡፡
. .
ይህ መንፈስ በጠበል ቦታ ራሱን የመደበቅና የመሰወር ከፍተኛ ችሎታ የለው ብቻ ሳይሆን የሚያስገርመው በጠበልና በተለያየ የአገልግሎት ሥፍራዎች ላይ እየጮኸና ወጥቶ የሄደ እየመሰለ በማዘናጋት የተዳፈነ እሳት ሆኖ ለጊዜው ውስጣችን ተረጋግቶ ጸጥ ብሎ መቀመጥ የሚችል መንፈስ መሆኑ ነው ፡፡
. .
ሌላው የረቀቀ ሥልቱ ደግሞ ራሱን በማመሳሰል እንደ ቅዱስ መልአክም ለመሆን እየቃጣው ንስሐ ግቡ ጫማ ከመግቢያ በር አውልቁ እያለ በጠበል ቦታና በአንዳንድ የጥምቀት ቦታዎች ገላጭ በመሆን የብዙ ክርስቲያኖችን ልቦና በመሳብ ውስጣዊውን የእግዚአብሔር አምልኮ
ጥንካሬያቸውን ያጠናል ይሰልላል ፡፡
. .
. ውጫዊ እይታን ማደናገር .
. .
የጠቋር መንፈስ ካሉት ክፉ ጠባያት መካከል አንዱና ዋናው ውጫዊ እይታን በማዘበራረቅ ልቦናን መረበሽ ነው ፡፡ ክፉው መንፈስ በዓይንና በልብ ውስጥ በማድፈጥ መንፈሱ ያለበት ሰው ለሚያየው ነገር ትኩረት እንዳይኖረው አድርጎ ያንን የተመለከተውን ነገር አዛብቶ በማቅረብ ልቦናውን በመረበሽ አእምሮውን ይበጠብጣል ፡፡
. .
. ውጫዊ ድምጾችን አጣሞ ማሰማት .
. .
ዘመድ ቤተሰብ ጎረቤት ጓደኛ ውስጥ ተንኮል እንደሚፈጽሙ አድርጎ ማሳየት ሳይናገሩ እንደተናገሩ አድርጎ ማሰማት ያላወሩትን እንደ አወሩ አድርጎ በማሳመን በክፉ እንድናስባቸውና እንደናያቸው ያደርጋል ፡፡
. .
, የእንስሳትን ድምጽና ጩኸት መተርጎም .
. .
. ከመንፈሱ ሥውር ወጥመዶች መከላከል ለምሳሌ : ጅብ ሲጮህ መቁጠር ወፏ ያለ ወትሮዋ ለየት ያለ ዝማሬ አሰማች ውሻው እንዲህ ብሎ አላዘነ ጉንዳን በስልፍ ሆኖ ወደ ቤት ገባ ወዘተ ... በማለት እየተረጎምን የሚመጣውን ጊዜ ከክፉ ነገር ጋር በማዛመድ በሥጋትና በፍርሃት ተቆራመደን እንድንኖር ማድረጉ አንዱ ነው ፡፡
. .
. . . ሌላ ሰው የማያየውን መመልከት .
. .
ጠቋር ዓይን ላይ በመቀመጥ በአንድ ሰው ላይ ያደረን ክፉመንፈስ በማሳየት ያስደምመዋል አንዳንዴም መላእክትን አስመስሎ በመናገር በብዥታ ውስጥ መልእክት ያስተላልፍለታል ፡፡
. .
. የሸክም ጫና መፍጠር .
" ጫንቃውን ከሸክም፥ እጆቹንም በቅርጫት ከመገዛት አራቅሁ።"
(መዝሙረ ዳዊት ፹፩:፮)
. .
የጠቋር ክፉ መንፈስ ከሌሎች ውቃቢዎች አውሊያዎችና ዛሮች ለየት የሚያደርገው በቀኝ ትከሻ ላይ ተቀምጦ ትልቅ ድንጋይ ወይም ከባድ ዕቃ የተሸከምን ያህል እንዲሰማን በማድረግ ብርቱ በትከሻ ላይ ድበታና ጫናን መፍጠር ሌላው የሚታወቅበት ገጽታው ነው ፡፡ ሌላው ችግር በትከሻ ላይ ወይም በጀርባ በኩል ሆኖ በብዥታ የቆመ ሰው መስሎ ገጽታውን ማሳየት የተለመደ ልዩ ተግባሩ ነው ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በአውላላ ሜዳ ላይ የቡና ሽታ ወይም የሽቶ መዓዛ በማምጣት የመንፈሱን የሽታ ፍላጎት ከሚሸተው ሰው ስሜት ጋር በማስተሳሰር የልብን አምሮትና መሻትን በሽታው መዓዛ አማካይነት እንዲናፍቅ ያደርገዋል ፡ ፡
. .
- ውስጥን ማድመጥ .
ውስጥን አዳምጦ በጎውን ነገር መሸሽ ፣ ውስጥን አዳምጦ ክፋትን መለማመድ ፣ ውስጥን አዳምጦ የሌሎችን ሕይወት ለመተናኮል መመልከት ፣ ውስጥን አዳምጦ አጋንንቱን ማገልገል እነዚህ ውጥን የማድመጥ ልምምዶች በብዙዎቻችን ሕይወት ውስጥ ሥር ሰደው ከተቀመጡ ቆይተዋል ፡፡ ምክንያቱም ቤተሰባችን ከቅዱስ ቁርባን ሀይልና ከመንፈሳዊ በረከት በመውጣቱና በመራቁ ነው ፡፡ በሌላ አነጋገር በዘራችን ውስጥ ዘልቀው ጣልቃ የገቡ ርኩሳን መናፍስት አብረውን ዘር ሆነዋል ፡፡ ስለዚህ ውስጣችን ስናዳምጥ ብዙ እንጎዳለን ፡፡
. .
ጠቋር ከውስጥ ሆኖ የነገረህን ሀሳብ የበለጠ እንድታምነው በሕልም አሳምሮና አስተካክሎ ያሳያል ፡፡ ከዚህ መተጨማሪም በስው ላይ አድሮ ያንኑ ሀሳብ ከሌላ ሰው አንደበት እንድትሰማው ሰው የዘጋጅልሃል ፡፡
. .
, የጠቋር መንፈስ በአውደ ነገሥቱ ከፍተኛ ቦታ የተሰጠውና ከስያሜው የተነሳ ታላቅ የተባለ ቆየት ብሎ ቀኝን በመያዝ ጠባቂ መልአክ የሚባል ልዩ ስያሜና ክብር የተሰጠው ነው ፡፡ ብዙዎች ሳያውቁት ተከትለውታል የአምልኮት ክብር ሰጥተውት በውስጥ በኩል የሚነግራቸውን እያዳመጡ ችግራችንን ይቀርፋልናል ብለው በጨላማው የአስተሳሰብ ስሜት ይመሩበታል ፡፡ ይህ የተሳሳተ የጥፋት መንገድ በትውልዳቸውም ውስጥ ቀጣይ ሆኖ አብሮ በመወለድ በተለያየ ዓይነት ሁኔታ ልጆቻቸው በመንፈሱ እርግማን እንዲፈተኑ ያደርጋቸዋል ፡፡
. .
'የጠቋር መንፈሰ ለሰዎች የሚያወርሳቸው አንዳንድ ጠባያት
. .
የጠቋር መንፈሰ አጋንንት እና ሰይጣን ቢሆንም ንግሥናውና የሚጠራበት ስም በዛሮችና በውቃቢዎች ዘንድ እንደ ትልቅ ማዕረግ ስለሚታወቅለት ራሱን ታላቅና ሀያል አድርጎ ይቆጥራል ፡፡
. . . መንፈሱ የሰው ልጆችን ሕይወትና ኑሮ የሚፈትንና ለፈተና አሳልፎ የሚሰጥ ወይም የሚዳርግ ክፉ የዲያብሎስ መንፈስ በመሆኑ አንዴ ውስጣችን ከገባ ባሕርያችንን ለውጦ እልከኛ ፣ ደፋር ፣ ጉልበተኛ ጠበኞ ትዕቢተኛ ቁጡና ሀይለኞ .. ወዘተ ስለሚያደርገው ሕይወታችንን ከሌሎች ሰዎች ጋር ያለንን መልካም ግንኙነት ሁሉ አደጋ ላይ በመጣል ያበላሻል ፡፡
. .
. ጭንቀትን መፍጠር .
" በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፥ ከመከራቸውም አዳናቸው፤" (መዝሙረ ዳዊት ፻፯:፮)
አእምሮአችን ውስጥ የእርሱን ውሳኔ የራሳችን ውሳኔ እንዲመስለን ያደርጋል ውሎ ሲያድር ግን ምን ሆኜ ነው እንደዚህ ዓይነት ውሳኔ የደረኩት ብለን እንድንጨነቅና ሕሊናችንን ክፉኞ እንድንወቅስ ያደርጋል ፡፡ በዚህ ሁኔታ መንፈሱ ከአእምሮ ከሕሊህና ከልቦናህ በአጠቃላይ ከራስህ ጋር እየተጣላህ እንድትኖር ስለሚያደርግህ ጭንቀት የማይለየው ሰው ትሆናለክ ፡፡
• የጭንቀቱ ዓይነቶች •
ሀ.ራስህ የምትደብቀው ጭንቀት ፣ የሚያስጨንቀው ጉዳይ የሚታወቅ ይሆንና ለምሳሌ ባል ለሚስቱ ሚስት ለባልዋ የማይገልጹት ይሆናል ፡፡
ለ.የተሰወረ ጭንቀት ፣ አስጨናቂው ፡ ጭንቀት ጭንቀት ይልሃል ፡፡
ሐ.የተገለጠ ጭንቀት ፣ የጭንቀቱ ጉዳይና ሁኔታ በደንብ ልታውቀውና ልትገልጸው ትችላለህ ፡፡ ነገር ግን ወደ መፍትሔ እንዳትሄድ ጭንቀትህን የሚያባብስ የሚጫንህ መንፈስ ይኖራል ፡፡
• የፍርሀት መንፈስን ማንገሥ •
" በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም። " ( መዝሙረ ዳዊት ፳፫ : ፬ )
. .
ሀ.የሥጋ ፍርሃት (ውጫዊ ) ለምሳሌ አውሬ ስናይና ከፍተኛ ድምፅ ሲጮህብን የሚፈጠርብን ድንጋጤ ከነባራዊው ዓለም ወይም አውጭ የሚመነጭ የሥጋ ፍርሃት ነው ፡፡ ዲያብሎስን ብዙ ጊዜ በሥጋዊ ዓይናችን የምንገነዘበውን ከመንፈሳዊ ጉዟችን ለማደናቀፍ ይህን ዓይነቱን ፍርሃት ያመቻችልናል ፡፡
ለ.የነፍስ ፍርሀት ( ውስጣዊ ) ከውስጣችን የሚመነጭ የፍርሀት አየነት ነው ፡፡ ነፍስን የሚያስፈራው ሀይል ደግሞ ዲያብሎስና ሠራዊቱ ነው ፡፡ቤታችንን ኑሮችንን ሀብታችንን ጤናችንን ... በአጠቃላይ ሕልውናችንን ረግጦ የያዘው ዲያብሎስ የውስጥ ፍርሀታችንና ጭንቀታችን ሁሉ መሠረት ነው ፡፡ ሐኪሞቻችንና ሌሎች የመስኩ ሙያተኞች ለሁሉም የፍርሃት ዓይነቶች ፎቢያ የሚል የጋራ መጠሪያ አበጅተውለታል፡፡
. .
. ለምሳሌ aqua phobia - ውሃን መፍራት
. Achluo phobia - ጭለማን መፍራት
. Avio phobia - የአውሮፕላን ጉዞን መፍራት
. gamo phobia - ጋብቻን መፍራት
. Ecclesio phobia - ቤተክርስቲያን መፍራት
. .
. የጠቋር መንፈስ የፍርሀት ጥላዎች .
. ይህ መንፈስ መንፈሳዊ መሠረት የሌላቸውንና ጾም ጸሎት ስግደት የማያውቁትን እንዲሁም ልማዳዊ አምልኮት የሚከተሉትን ሰዎች በማስፈራራት የሚበረታ ሲሆን በዓይን-ሕሊናቸው በፍርሃት እንዲዋጡ በብዥታ ማደናገርና ከዋላቸው ጥላ መስሎ በመቆም በመክበድ በበላያቸው በማንዣበብ ሰውነታቸውን በመጎንተልና ማስደገጥ የልብ መራድና የአእምሮ መጨነቅን በመፍጠር ወደ እብደት የሚወስደውን የአእምሮ ሕመም እንዲፈጠርባቸው ያደርጋል ፡፡
. .
. በአጠቃላይ ይህ የድፍረት መንፈስ የሰው ልጆችን ሕይወትና ኑሮ እየፈተነ በስኬት በእድገት ጎዳና ላይ እንዳይረማመዱ አድርጎ ወደ ጨለማ የሚመራ ቢሆንም በእምነት ሀይል እግዚአብሔር በሰጠን የእግዚአብሔር ልጅነት በምሕረቱና በቸርነቱ ጥላ እየታገዝን በቅዱሳን መላእክት እርዳታ በፃድቃን መንፈስ ምልጃ እየተረዳን በቅዱስ ወንጌል የቃሉ ብርሃን እየተመራን በክርስቶስ ሥጋና ደም ስንታተም ይህንን ጠላታችንን ከሕይወታችንና ከዙሪያችን ልናስወግድበት የምንችልበት ሀይል እግዚአብሔር ይሰጠናል ፡፡
" አንተ መብራቴን ታበራለህና፤ እግዚአብሔር አምላኬ ጨለማዬን ያበራል።በአንተ ከጥፋት እድናለሁና በአምላኬም ቅጥሩን እዘልላለሁ።"
. መዝሙረ ዳዊት ፲፰ : ፳፰ - ፳፱
ምንጭ "በማለዳ መያ`ዝ መጽሐፍ" ✞ በመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ
!!! እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ በቅርቡ ቀን !!!
☞ ክፉ መናፍስቶችን የማዋረስ ምሥጢራዊ ጥበብ

የዝሙት መንፈስ ምንድነው? አይነጥላ ምንድነው?