Tuesday, September 19, 2017

ሙስሊሟዋ ድንቅ ተዓምር በሸንኮራ ዮሐንስ ተደረገላት

" ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል። በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል።ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎችን ወደ ጌታ ወደ አምላካቸው ይመልሳል " ሉቃ.1፡14
ሸንኮራው ቅዱስ ዮሐንስ ድንቅ ተአምር
ሃይማኖቴ "ወልድ ፍጡር፣ ቤተክርስቲያን ድንጋይ ናት" ሎቱ ስበሐት ። ከሚሉ አሕዛብ ወገን ነበርኩ የምትለዋ እህታችን መኖሪያዋ በመዲናችን አዲስ አበባ ነው ። ክርስቲያን የሚባል አልወድም፣ ፍጹም ጥላቻንም የተሞላው ነበርኩ። አምላኬን ያስደሰትኩ መስሎኝ አንድ አብሮ አደግ ክርስቲያን ጓደኛ አለችኝ። ብሰድባት ብተፋባትም ጉዳይዋ አይደለም ኣትቀየመኝም። ቅዱስ ዮሐንስን በጣም ትወደዋለች።
እኔ በስኳር በሽታ ምክንያት አንድ እግሬ በጋንግሪን (የተወሰነ አካል መሞት) እንዲቆረጥ ሐኪም ወሰነ። ያች ጓደኛዬ ግን የዮሐንስ ጸበልን ቤቴ አመጥታ ሰጠችኝ። ተቀብያት ከፊቷ ይህ እኮ "ውሐ" ነው ተረት አታውሪ ብዬ ስደፋው የጸበል ዕቃውን የያዘ እጄ ሰለለ ሽባ ሆነ፤ ደነገጥኩኝ። የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ። አይዞሽ ምልክት ነው መጥምቁ ያማልድሻል አለችኝ። "ኦፕራሲዮኑን ተይው አንቺ ካልዳንሽ እኔ ሃይማኖቴን እቀይራለው" ስትል ቤተሰቤ በሃሳብ ለሁለት ተከፈለ። እግሬ በአስቸኳይ ይቆረጥ ተብሏል። እግሬም ቁስሉ ሽታ አመጣ። በዚያ ላይ በሃይማኖቴ፣ ቤተሰቤ ሁሉ በአይነ ርግብ ተሸፍኖ የሚሄድ ነው። መገላለጥ የለም፤ "እዛ ብትሔጂ እንረግምሻለን" አሉኝ። በመጨረሻ ውሳኔ የኔ ሆነና ከሶስት ቤተሰብና፣ ከዚህችው ወዳጄ ጋራ ሸንኮራ ሄድን። ወደ ጸበሉ መውረድ አልቻልኩም አምጥተው አጠመቁኝ። ቁስሉ እንደቅርፊት ወደቀ። እንደውም ጸበሉን የደፋሁበት እጄ ዳነ። የምን መቆረጥ የምን ጋንግሪን።
የሕመሜም ምክንያት የነበረው 23 አመት ያሰቃየኝ ስኳሩም ዳነ። አብራኝ የሄደች አንድዋም ቤተሰቤ በፍንጢጣ ኪንታሮት ትሰቃይ ነበር የባህል መድሐኒት ወስዳ ጽኑ ህመም ላይ ነበረች እርስምዋ ዳነች።በሰማዕትነት ለአምላኩ ምስክር የሆነው መጥምቁ ዮሐንስ ከአምላክ አማልደህ ካዳንከኝ ጥላ በሬ ላምጣ አልልም አንተ ምስክር ለሆንክለት “በክርስቲያን አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለው” ብዬ ነበር።
ይህም ድኜ ለስዕለቴ በቃው ከስምንት ቤተሰቤ ጋር ሃብተ ወልድና ስመ ክርስትና ተቀበልኩኝ። ትለናለች።
እህተ ዮሐንስ፤ፍቅርተ ዮሐንስ፤ወለተ ብርሐን፤ተጠምቀ መድህን፤ክፍለ ዮሐንስ፤ገብረ ዮሐንስ፤ወልደ ዮሐንስ፤አርከ ዮሐንስ ተብለን የቀራኒዮ ቤዛ ወደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ነቢይ ሳይሆን አምላክ እንደሆነ አምነን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቀናል።
ቅዱስ ዮሐንስም ተአምር ግን ድሮ ነው የጀመረው ጎረቤቴ ዝክሩን ስታደርግ አትጥሪኝ እላት ነበር። ዝክሩንም አልበላም ጣኦት አምላኪ አድርጌ ነው የምቆጥራት። የክርስቲያኖች አምላክም ብዙ ነበር የሚመስለኝ። አወይ አለማወቅ በድብቅ ግን ዝክሩን በልጆች ስም አስመጥቼ እበላ ነበር።ይጣፍጠኛል ለካ በስተመጨረሻው የሕይወት እንጀራን ስጋ ወደሙ ሊያበላኝ ኖሯል እንዲያ የጣፈጠኝ፤ ትላለች እህታችን በጥምቀቱ ስነ ስርአት በዓይኔ በአካል ተገኝቼ በከተማችን በሚገኝ አንድ አጥቢያ ተከታትያለው ይለናል አንተነህ ሐይሌ።
እኛ የእምነት አቃቂር ስናወጣ ጥቅስ ስናገላብጥ የዛሬ 2000 አመት አንገቱ የተቆረጠው መጥምቁ ዮሐንስ ስንት የጠፋውን መንጋ ጥቅስ ሳይጠቅስ ቃላት ሳያዥጎደጉድ በፍቅሩ አስሮ በምልጃው ጠብቆ ለጌታው ምርኮን አስገባ። ይህን ያደረገ የመጥምቁ አምላክ ክብር ይግባው ዮሐንስ ነቢይ ሰማዕት እኛንም ያማልደን አሜን።
ከአንተነህ ኃይሌ ገጽ ተገኝቶ ጥቂት እርማት የተደረገበት የእውነት ምስክርነት። ወደፊት ግለሰቦቹ አነጋግረን የበለጠ መረጃ ለማድረስ እሞክራለሁ። “ እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።”ሉቃ 15:7

Wednesday, August 30, 2017

የሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ድንቅ ተአምር

በደቡብ አፍሪካ ደርባን ያደረገው
ጥ ብልው ቁጭ እንዳሉ ቡኒ የፓሊስ ልብስ የለበሰ ቀይ ወጣት እናቴ አትፍሪ ምን ሆነሽ ነው አትፍሪ ፓሊስ ነኝ ይላቸዋል ወዲያው አንድ እብድ ድንጋይ ወርውሮ የሱፐር ማርኬቱን መስታወት ይሰብራል ያ ድንጋይ ናድያ ቀሚስ ላይ ቁጭ ይላል ወደውስጥም ዘልቆ አትፍሪ አዕምሮውን የሳተ ሰው ነው ብሎ ያረጋጋቸዋል ዘጠኙ የስራ ባልደረቦቻቸው ሲመጡ በሆነው ነገር ይደነቃሉ ፓሊስም ስላዮ ደስታቸው እጽፍ ሆነ ሆቴላቸው በር ደርሰው አስፓልት ሊሻገሩ ሲሉ ናዲያ ብሎ በስማቸው ጠርቶ ይጨብጣቸውና የት ይግባ የት አያስተውሉም ዘጠኙ ሰዎች የራሳቸውን ጨዋታ ይዘዋልና አላስተዋሉም ያው ነጭ ፓሊስ አግኝታ ወሬ ይዛለች ብለው ትተዋቸዋል ሆቴሉ በር ላይ ላሉት ሴኩሪቲዎች ሲነግሩዋቸው ቡኒ ልብስ እኛ ሐገር የሚለብስ ወታደር የለም ጉዳዮን ለደህንነት ክፍሉ ያመለክታሉ እንዲህ አይነት ሰው አናውቅም ይህ ኢኒፎርምም የለንም ስለተፈጠረው የጥበቃ ክፍተት ይቅርታ ይጠይቃሉ መጀመሪያ አልፈዋቸው የሄዱት ወንበዴዎች 5 ሰው እዛው መንገድ ገድለዋል በዛው ቅጽበት ከዘጠኙ 8 ኢ አማኒ ናቸውና አልተገረሙም መኝታ ክላቸው ገብተው እጃቸውን ሲያዮት በቅባ ቅዱስ እርሶዋል ለካ ናዲያ ብሎ በስሜ የጠራኝ በእግሊዘኛ ሳይሆን በአረብኛ ነበር ያወራኝ ታዳጊው ሰማዕት ነው ይህ እንዴት ይሆናል ብለው ያነባሉ ምስጋናም ያቀርባሉ እዛው ደቡብ አፍሪካ በተመሳሳይ በሌላ አመት ቅዱስ መርቆሬዎስ በገሐድ በመገለጥ ከአደጋ ታድጎዋቸዋል ይህ ታምር ሲሰራ ወላጅ እናቴም ነበረች ይህች ሴት ይህን ነጭ የት አውቃ ነው የሲአይ ኤ ሰላይ ሳትሆን አትቀርም እዛ ኮንፍረንስ ሞል ስንፈራ ስንቸር ለምን አልጠራችውም አሁን ከየት መጣ ደግሞ ሱፐር ማርኬቱ ውስጥ ሳየው አይኑ እሳት ይመስላል ኩዋሱ አይታይም እያልኩኝ አምቻለው ብላኛለች በወቅቱ ስለ እምነት ብዙ ዕውቀቱ ባይኖረኝም የሴኩሪቲዎቹ አናውቀውም ማለትና ሳይሰናበትን መሄድ ገርሞኛል ብላለች ይህ ምስክርነት በአሮጌው ካይሮ በሚገኘው የሰማዕቱ አቡ ሰይፌን ገዳም በተአምራቱ መዝገብ ላይ አጽፈውታል ድንቅ አድራጊው ሰማዕት ከነፍስና ስጋ አጥማጅ ክፉ መናፍስት ምልጃው ይታደገን አሜን ለአምላከ መርቆርዬስ ክብር ይግባው እልልልልልልልልልልልልልልልልልል

በወረብ አብሮ የሚሳተፈው የቅዱስ መርቆርዮስ ስዕል

Sunday, August 27, 2017

122 አመት የሆነው ታቦተ አቡነ አረጋዊ በተኣምር ተገኘ

ሰላም እንደምን አላችሁ፡ 21/12/2009ዓ.ም በ ሎዛ ማርያም ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን(ብርጭቆ ማርያም) ለአገልግሎት ነው የሄድኩት ቅዳሴ ካለቀ በኀላ ተአምረ ማርያም ተነቦ በአውደ ምህረት አንድ አባት ፦ ነሀሴ 7ቀን በቤተልሔሙ ጋር ብርሀን አይቻለው አንድ ነገር ይኖራል ስለዚህ ቆፍረን ማየት አለብን ብለው ለ አለቃው ይነግሯቸዋል እሳቸውም እሺ በማለት ከ አባቶች, ዲያቆናትና ምእመን ባለበት ሲቆፈር የ ብረት ሳጥን በ ፎቶ እንደምታዩት ብዙ መስቀል ፡ ጽና፡ ማዕጠንት፡ እናም ታቦተ አቡነ አረጋዊ እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ሆኖ በ አልባስ ሆኖ ተገኘ፡፡ ሳጥኑ ላይ በ1878 ዓ.ም ተብሎ ተጽፎበታል ማለትም ወደ 122 አመት የሆነው ነው፡ እግዚአብሄር ይመስገን በ ህይወቴ ለመጀመሪያ ግዜ እንዲህ ሲገጥመኝ፡፡ ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በረከታቸው ይደርብን አሜን፡፡












Sunday, March 26, 2017

ዘብር ቅዱስ ገብርኤል


በሰሜን ሸዋ በመንዝ በላሎ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ የመላዕኩ የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አለ ይህ ቤተክርስቲያን ዘብር ቅዱስ ገብርኤል ሲባል መስቀልና መቋሚያ ተቆሞ የሚፀለይበት አስደናቂ የፈውስ ቦታ ነው። በዚህ ቤተክርስቲያን ከ50 ዓመት በላይ ደብሩን ያስተዳደሩ የበቁ አባት የ103 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ኤኔታ አክሊሉ ይገኛሉ ። በዘመናችን እግዚአብሔር ካስቀመጠልን የፀሎት አባት የብቃት ደረጃ ላይ ከደረሱ አባቶች መካከል አንዱ ናቸው ። ኤኔታ አክሊሉ ኮርያ ከወንድማቸው ጋር ዘመተዋል በዚያም በጦር ሜዳ ከወንድማቸው ጋር ስዕለት ተሳሉ፤ስለቱም በሰላም ለሀገራችን ቃበቃህን ዕድሜ ልካችንን በድንግልና በክህነት እናገለግላለን ብለው ለዘብር ገብርኤል ተሳሉ እግዚአብሔርም ሰለታቸውን ሰምቶ እንቅፋት ሳይመታቸው እሾክ ሳይወጋቸው በሰላም ወደ ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጰያ ተመለሱ ። ኤኔታ አክሊሉም በስዕለታቸው መሰረት በክህነት ዘብር ማገልገል ጀመሩ ወንድማቸው ግን ስዕለቱን ወደ ጎን በመተው ሚስት አገባ ኤኔታም ወንድሜ ነው ዘር ይተካ ሳይሉ ወንድማቸውን ጠርተው ይህ በአንተ ዘንድ አይደረግ ስዕለትንም አትርሳ ብለው ወቀሱት ንስሀ ገብቶ አብሮ በክህነት እንዲያገለግል መከሩት እርሱ ግን አሻፈረኝ ብሎ እምቢ አላቸው ወድያውም ሚስቱ ሞተች ፤ እርሱም የጥፋት ሰው ነውና ድጋሚ ሌላ ሚስት አገባ ኤኔታም እጅግ አዝነው ተቆጡት ምክራቸውንም አልሰማ ሲል በመጨረሻ ወንድማቸው ራሱ ሞተ አባታችንም አልቅሰው ቀበሩት። ኤኔታ አክሊሉ በዘብር አገልግሎታቸውን ቀጠሉ በእጃቸው የተማሩ ከ55ሺ በላይ ሊቃውንት አፈሩ ፣ኤኔታ የማያውቃቸው የቤተክርስቲያን ሊቅ የለም በመላው ኢትዮጰያ ያስተማሯቸው ሊቃውት እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደምድር አሸዋ የበዙ ናቸው ፣አሁን ከ400 በላይ የቆሎ ተማሪ በስራቸው ይገኛል በዚህ ተጋድሎቸው የተመለከተው ጠቅላይ ቤተክህነት የጵጵስና ማዕረግ ሊሰጣቸው ጥሪ አቀረበላቸው እርሳቸው ግን በኮሪያ የገቡትን ቃል አስበው አልፈልግም ዕድሜ ልኬን ዘብር ገብርኤልን ላገለግል ስዕለት አለብኝ ብለው የክህነት ሹመቱን መለሱት፤ እውነተኛ አገልጋይ የቤተክርስቲያን ባለውለታ ድንቅ አባት ናቸውና ።

አንዴ እንዲ ሆነ ኤኔታ አክሊሉ ተማሪ በሚያስተምሩበት ጊዜ ተማሪያቸው እየሞተ ተቸገሩ ሀገሩ ላይ ታላቅ መቅፀፍት ሆነ በዚህም የተነሳ አባታችን ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው የፃድቁ አባታችንን የአቡነ አብተማርያምን ታቦት ተሸክመው ወደ ዘብር ገብርኤል ይዘው መጡ ኤኔታ አክሊሉ የአብተ ማርያም ቃል ኪዳን መቅሰፍት አራቂነት ጠንቅቀው ያቃሉና ታቦቱን ከመንበሩ ቢያስቀምጡት መቅሰፍት ከአገሩ እርቆላቸዋል አንድም ተማሪ ከዚያ በኃላ ሞቶባቸው አያውቅም። ኤኔታ የሚሞቱበትን ቀን የሚያቁ ሲሆን ወደእርሳቸው የሚመጣውን ሰው ማንነት የማወቅ ፀጋ አላቸው ማህራችን ላይ ዘብር ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ከአዲስ አበባ እንደሚመጣና ቤተክርስቲያኑን በዓለም ደረጃ የሚያስተዋውቅ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን ትንቢታቸውም ተፈፅሞ በክብር ተቀብለሁን እኛም የማንጠቅም ባሪያ ስንሆን ገዳሙን በዓለም ደረጃ አስተዋውቀናል ኤኔታ አክሊሉ የፀሎት አባት ሲሆኑ ምግባቸውም አጥቢት እና አጃ ብቻ ነው እርሷን ለቁመተ ስጋ ነው የሚመገቡት፣ አንድ ጊዜ እርሳቸው ቤት ገብቼ አልጋቸው ላይ እንድቀመጥ አደረጉኝ ስለቤተክርስቲያኑ አንዳንድ ነገር ለመነጋገር በዚያ ጊዜ ብዙ ክርስቲያኖች በእጃቸው መስቀል ለመሳለም ቤታቸውን አጨናንቆት ነበር ቤቱ ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ ከአራት ሰው በላይ ማስተናገድ አይችልም ሰው ውስጥ ተጨናንቆ ገብቶ ቀሪው ውጪ ጋር ተራ እየጠበቀ ሰልፍ ይዟል በመሀል የወረዳው ፀሐፊ መርጌታ ጥላውን የሕዝቡን መጨናነቅ የቤቱን ጥበት ተመልክተው ከበር ሊመለሱ ሲሉ ኤኔታ አክሊሉ ሰው ሳይጋርዳቸው ግድግዳ ሳይሸፍናቸው ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ና አንተ የወረዳው አትመለስ ግባ ብለው መጥራታቸውን የወረዳው ፀሐፊ ደንግጠው የገቡበትን ቀን አረሳውም አርባራ መዳኒዓለም ቤተክርስቲያን ከሽቦ አጥር በኃላ ምንም ነገር አይነሳም አንዲት እህታች የሾላ ፍሬ አንስታ ቦርሳዋ ውስጥ ብትከት መኪናችን ሶስት ጊዜ ጎማ ፈነዳብን በዚህ የተነሳ በጣም ተጨንቀን ሳለ እህታችን የሾላ ፍሬ ከቦርሳዋ አውጥታ እኔ ከተከለከለ ቦታ አንስቼ ነው ብላሰጠችን እኛም ፀሎት አድርገን ምሕረቱን እንዲያደርግልን ተማፅነን ጎማችንን አስተካክለን ተነስተን ዘብር ገባን እኔም ወደ እኚ የበቁ አባት ጋር ለመባረክ አቀናው ወደያው ሲያዩኝ እየሳቁ አጠገባቸው እንድቀመጥ አድርገው የሆነውን ነገር ቦታው ላይ እንደተገኙ አድርገው የደረሰብንን መከራ ራሳቸው መናገር ጀመሩ እኔ እጅግ ደነገጥኩኝ እሳቸው አይዞ መላዕኩ ከእናንተ ጋር ነው ብለው አረጋጉኝ ይህንን ቀን መቼም ቢሆን አረሳውም በእውነት በእሳቸው እጅ መባረክ መታደል ነው ክብራቸው ቢረቅብን ከግሪክ ሀገር የክህነት ልብስ አስመጥተን ብሰጣቸው ለእናንተ ስል ለአንድ ቀን እለብሰዋለው ብለው አንድ ቀን ስለፍቅር ለብሰው በነጋታው የኬሻ ቆባቸውን አደረጉ። የዚህችን ዓለም ጣዕም ንቀዋልና አይናቸው ከፀሎትና ከእንባ ብዛት የተነሳ ደክሟል የፃድቅ ክብሩ የሚገለጠው ሲሞት ነውና ያልተነገረ ብዙ አለና ወደ ሀገራቸው ከመሄዳቸው በፊት በረከታቸውን እናግኝ መልክቴ ነው በቀጣይም ስለ በረሃው አባት አባ ላዕቀ ስለ ኢትዮጰያ የተናገሩትን እና ያጫወቱኝ ታሪክ ይዤላችሁ እቀርባለው አስከዛው ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን አሜን

Wednesday, February 8, 2017


ዛሬ የአባታችን የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ የድህነትን ስጦታ ስለተቋደሰች እህታችን ላይ የተፈፀመውን ድንቅ ታምር ላውጋችሁ፣ ከስር ፎቶው ላይ የምትመለከቷት እህታችን በጡት( thoracic cancer) ካንሰር ደዌ ተይዛ ለዘመናት በመፍቴህ አልባ እንቅስቃሴ የአለም ሆስፒታሎችን በር በማንኳኳት ስትዳክር ቆይታለች ።ከሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ ባሉ ስመጥር የህክምና ዶክቶሮች ዘንድ በመቅረብ ለችግሯ መፍቴህ የሚሆናትን መንገድ ስታፈላልግ ብትደክምም አንዳቸውም ከስቃይዋ ሊያሳርፏት አልቻሉም ። ባላት ሙሉ አቅም መነካት እና መደረስ አለበት የተባሉትን ሁሉ ብትነካም የበሽታው ህመም እና ስቃይን እንዳያድግ ከማድረግ አላገዳቸውም ።ኑሮዋ በስቃይ ላይ ስቃይ በህመም ላይ ህመም የሆነላት ይህች እህታችን ግን በአንድ ወቅት ከአንድ ወዳጇ ታምራዊ ፀበል ከወደ አርባምንጭ እንደፈለቀ እና ብዙዎች በመጠመቅ እንደተፈወሱ በመንገር አይኗን ገልጣ ሞትን ከመጠባበቅ እድሏን እንድትሞክር ይነግሯታል።እሷም ይህን ጥሪ ችላ ለማላት ባትፈልገውም ልሞክረው በሚል ሃሳብ ወደ ስፍራው (ዝጊቲ አርባምንጭ) ትመጣላች ።በተፀበለችው ቀናት ሁሉ በሽታው ከሚያደርስባት ስቃይ እና ህመም ማገገም እና ማረፍ ጀመረች ።ከጥቂት ሱባኤ በሃላ የልዑል እግዚአብሄር የማዳን ፍቃድ በአባታችን አቡዬ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፀበል ላይ በመስፈፍ እህታችንን ሙሉ በሙሉ ከበሽታዋ እንድትድን እና እንድትፈወስ አደረጋት። ይህንንም በአለም የህክምና ምርመራ በማረጋገጥ የአቡዬን ድንቅ ስራን ለአለም በመስበክ ምስክርነቷን በተለያዩ ጉባኤዎች ላይ ሰጥታለች ።ይህን የአባታችንን ውለታ የማይረሳ ልብ ያላት እህታችን ከሞት ፅልመት በፈውሳቸው ጎትተው ላወጧት አባታችን ውለታ በማሰብ የደብሩን ህንፃ ቤተክርስትያኑን ብቻዋን በአዲስ መልክ ለመስራት በማቀድ እና በማሰብ የ20 ሚሊዬን ብር የቤተክርስትያን ዲዛን በማሰራት እና ግንባታውን በመጀመር በስራ ላይ ትገኛለች ።
 

Tuesday, February 7, 2017

የቁልቋል በር ማርያም ቤተክርስቲያን


እነሆ ከተወለደ ጀምሮ 15 ዓመት ሙሉ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ ይኖር የነበረ ወንድማችን በእናታችን ጸበል እነሆ ከደዌው ተፈውሷል እንዲሁም ተነግሮ የማያልቅ ድንቅ ታምራት በእመቤታችን ተደርጓል የእናታችን የቁልቋል በር ማርያም ወዳጆች እንደሚታወቀው የእናታችን ቤት ለመጨረስ የተለያዩ ገቢ ማሰባሰቢያ እያደረግን እንገኛለን የተለያዩ ጉዞዎች ፣ ትኬቶችን በመሸጥ ላይ ነን፤ ይህን መልካም ስራ ለመስራት እናቴ ቤትሽ በፍሶ እኔ እንዴት በተደላደለ ቤት እኖናራለን ብለን ከሀገርም በውጪም የምንኖር እጆቻንችን ዘርግተናል በመዘርጋት ላይም ነን ታዲያ ቤተክርስቲያኑ በአሁኑ ሰዓት ስራው የጀመረ ሲሆን ነገር ግን አሁን ሙሉ ለሙሉ ስራውን ለመስራት እነዚ ነገሮች ይጎድላሉ እንደ አሽዋ ሲሚንቶ ፌሮ፣ እና ህንፃ ቤተክርስቲያኗን ለመጨረስ የሚያስፈልጉ ነገሮች በጣም ይጎድላሉ ከዚህ በተጓዳኝ ደግሞ ይህን ስራ የሚሰሩ ሳተኞች የሚከፈላቸው ብር ሙሉ ለሙሉ ባለመገኘቱ በተወሰነ ሰራተኛ ነው አሁን ስራው የተጀመረው በሀገርም በውጪም የምንገኝ እህት ወንድሞቼ አንዳችን ባንችል እንኳ ሁለት ሦስት ከዛ በላይ በጋራ በመሆን ያለንን በማዋጣት የእናታችን የቁልቋል በር ማርያምን ቤት እንስራ ከዛ ባሻገር ደግሞ ብዙ ምህመን እንደዚ ያለ ቤተክርስቲያን የለም እናንተ በስሟ ልትነግዱ ነው የሚል ሃሳብ ነበር ነገር ግን እውነታን ቦታው ድረስ ሄዳችሁ ያያችሁ እህት ወንድሞቼ ምስክር ናችሁ ከእናታችን ጎን በመሆን እጅ ለእጅ ተያይዘን የጀመርነው ከግብ እናድርስ፤ እማማ ወላዲተ አምላክ ያሰብነውን መልካም ነገሮች ሁሉ በምልጃዋ ታስፈጽምልን የባንክ አካውንት ቁጥሩ kuli kual ber d/m/k mariam b/k commercial bank of Ethiopia Acc/no 1000167540949 ለበለጠ መረጃ ደግሞ በህነዚህ ስልክ ይደውሉ 09 38 59 49 03/0911 76 28 72 / 0913 67 78 91 ደውለው ስለ ቤተክርስቲያኗ ያለችበት ሁኔታ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ ፡፡
‹‹ በእውነቱ ይህ ቤት ፈርሶ እናንተ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ልትኖሩ ጊዜው ነውን? ›› ሀጌ 1፡4

Monday, February 6, 2017

ፃድቃኔ ማሪያም ድንቅ ታምር

የእናታችን የፃድቃኔ ማሪያም ድንቅ ታምር ትላንት ለሊት እለተ ቅዳሜ ከለሊቱ 8:--- ገደማ እህታችን ጉሮሮዬን ተናነቀኝ ብላ መፀዳጃ ቤት ሄደች አብረዋት ያሉትም ሰዎች ተከትለዋት ይወጣሉ ታዲያ ያልታሰበ ክስተት ተፈጠረ አነቀኝ ባጠጠኝ ያለችው ይህ የምታዩት ቁወቱ አንድ ስንዝር የሚሆን እባብ ከሆዷ ወጣላት የድንግል ማሪያም ስም ይመስገን ክብር ለስሟ ይሁን ይህ ድንቅ ታምር የተደረገው በትላንትናው ለሊት እለተ ቅዳሜ ለእሁድ አጥቢያ ከለሉቱ 8:19 /26/5/2009 ነው እኔም ድንግል ማሪያም የዘረያእቆብ እመቤት ስውሯ ፅላት የአይን ምስክር ስላደረገችን ድንቅ ታምሯን እንድመሰክር ስላደረገችኝ ምስጋና ይድረሳት ለተጨነቅነው ሁሉ ትድረስልን አሜን


Wednesday, February 1, 2017

የእመቤታችን ድንቅ ተአምር

ከዚህ በታች የምታነቡትን ድንቅ ተአምር ያደረገችው የእመቤታችን ስዕለ አድህኖ በሀገራችን በኢትዮጵያ ሰበታ ቤተ ደናገል ጠባባት አንድነት ገደም (ጌቴሰማኔ ማርያም) የሚገኝ ሲሆን ምስለ ስእሏን በ ፎቶም ሆነ በቪድዮ ማንሳት ለክብሯ ሲባል የተከለከለ ነው፡፡ ይህ የምታዩት ግን እዛው ሰበታ መድኃኒአለም ቤተክርስትያን ውስጥ ይገኛል፡፡ ይህችን ተአምረኛ ምስለ ስእል እንዴትና ማን እንዳመጣት እንዲሁም የሰራችውን ተአምር እዛው ሄደው እንዲሰሙና እንዲያዩት እጋብዛለሁ፡፡
(በድጋሜ ፨ እባካችሁ አንተ ታዲያ ፎቶውን እንዴት አነሳኽው ለምትሉ፤ ይሄኛው ሌላ ነው አሳሳሉ ግን ይሄን ታሪክ መሰረት አድርጎ ነው። ተአምረኛዋ ምስለ ስዕል ግን አንድ አጥማቂ አባት (ቡኃላ አቡነ የተባሉ) በቦርሳቸው ይዘዋት ይዞሩ የነበሩ የጣሊያን ጦር ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጥይት ያልጎዳት መጽሐፍ ቅዱስ ነው ምታክለው። ገዳማውያን እናቶች አክብረው አስቀምጠዋታል)

ተአምሪሃ ለእግዝዕትነ ቅድስት ድንግል በ ፪ኤ ማርያም ወላዲተ አምላክ ጸሎታ ወበረከታ የሃሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን ልመናዋ ክብሯ በእኛ ለዘላለም በውነት ይደርብንና አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች ክብርት እመቤታችን ያደረገችው ተዓምር ይህ ነው። አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች ክብርት እመቤታችን በሥዕሏ አድራ ያደረገችውን ተዓምር ስሙ ።
ከአፍርንጊያ አገር ( ከአፍሪካ )ማለት ነው በከበረ ልብስና በወርቅ በብርም እጅግ የከበረ አንድ ነጋዴ ነበር ። ያም ሰው ሥጋ የለበሰች የምትመስለውን አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች የክብርት እመቤታችንን ሥዕል ዜና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው ። ገንዘቡን ሁሉና ንግዱንም ትቶ ደኃ መስሎ ወደ ጼዴንያ አገር ሄደ ሥዕሏንም ሠርቆ ወደ አገሩ አፍርንጊያ (አፍሪካ) ይወስዳት ዘንድ ይህንን ምክኒያት አደረገ ሥዕሊቱንም አግኝቶ ወደ አገሩ ይወስዳት ዘንድ የተጠረገ መንገድን ሊያገኝ ደጅ እየጠና በጼዴንያ የተሠራች የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ዓመት ያህል ሲያገለግል ኖረ ። እመምኔቲቱ ግን የመነኮሳቱን በር በፍፁም ትጋት ትጠብቅ ነበርና ሥዕሊቱን ይወስዳት ዘንድ እንዳልተቻለው ባወቀ ጊዜ ሾተልን ይዞ እጁን በመስኮት አዝልቆ ከሥዕሊቱ የሥጋ ቁራጭን ያህል ቆረጠ ያን ጊዜም ከሥዕሊቱ ደም ወጣ ። እርሱም የሥጋ ቁራጭን ያህል ይዞ ወጥቶ ተሠወረ ። ያን ጊዜም ሰዎች አውቀው በጭንቅ ፈልገው አግኝተው ያዙት ይገድሉትም ዘንድ ወደዱ ። ያን ጊዜም ከሥዕሊቱ እንዲህ የሚል ቃል ተነገረ "" እኔን ስለ መውደዱ ክብር ሊሆነው ወስዷል እንጂ ይህንንስ በክፋት አላደረገውምና ተዉት አትግደሉት ነገር ግን የተቆረጠውን ሥጋ ከእርሱ ወስዳችሁ ከተቆረጠበት ቦታ ግጠሙት "" ያን ጊዜም እንዲሁ አድርገው አኖሩትና ሥጋው ተጣብቆ ቀድሞ እንደነበረ ሆነ ነገር ግን የደምና የሾተሉ ፍለጋ ምልክቱ እስከዛሬም ድረስ ታውቆ ታይቶ ይኖራል ። በአርያም ለሚመሰገን አምላክን በወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ በፀናች በክብርት እመቤታችን አማላጅነትም ይህንን ተዓምር ለገለጸ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል ። ልመናዋ ክብሯ አማላጅነትዋ የልጅዋ የወዳጅዋም ቸርነት በእኛ ለዘለዓለም በውነት ይደርብን ። አሜን

የእመቤታችን መቃብርና ያረገችበት ጣራ - Tomb of The Virgin Mary

"የጎጆዋ አርሴማ" - ድንቅ ነገር


☞ እንሆ በአዲስ አበባ በቦሌ ቡኒ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነ ድንቅ ነገር !!!!!! እንዲህ ሆነ በ ጥር 10 2009 ዓ ም የጥምቀት በዓለ ክብር ከተራውን ፈጽመን እንሆ በ 13 የቅዱስ እግዚአብሄር አብ , ቅድስት ኪዳነምህረት ,ተክልዬ, አና አርሴምዬን አጅበን ወደ መንበረ ክብሩ ደረስን ስርአተ ቤተክርስቲያኑን አከናውነን በእግዚአብሔር ፈቃድ እና በአባቶች ራዕይ ጽላቷ የመጣችው ቅድስት አርሴማ በድጋሚ ከገዳማውያን አባቶች የተነገሩትን መልእክት በአውደ ምህረት ተናገሩ እንዲህ አሉ "ሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ጥንታዊ ለዛ ያለው ጎጆ ቤተክርስቲያን ሰርታችሁ በዛ አስገቡኝ " ብላለች ብለው ራዕዩን ተናገሩ ፡፡





ከዚህ በኀላ ማሳረጊያ ጸሎት ተደርጎ ታቦታቱ ወደመንበረ ክብራቸው ሲገቡ የቅድስት አርሴማን ያከበሩት አባት ተፍገመሙ ምን አልባት እረጅም መንገድ ስለተጓዙ ይሆናል በሚል ሌላ ካህን ተቀየሩ እንዲሁ እኒህ አባት ተንቀጠቀጡ በዚህ ጊዜ ምዕመናን በለቅሶ በዋይታ ተንበርክከው ማልቀስ ጀመሩ በዚህ ጊዜ ካህኑ ወደ ኀላ መልሳቸው እኛም ታቦቱን በማጀብ በእግዞታ ተከተልን በቅጽረ ቤተክርስቲያኑ ውስጥ በስተ ምስራቅ በኩል በጣም ቆንጆና ደልዳላ ቦታ ላይ ስትደርስ ካህኑን አቆመቻቸው በዚያች ቦታ ጸሎት ተደርጎ መሰረት ተጣለ ፡፡ ከዚህ በኀላ በነባሩ ቤተክርስቲያን በረንዳ ላይ ድንኳን ተጥሎ ታቦቷ በዛ አደረች እስካሁን በዛው ትገኛለች ፡ በአለቱ በተገኘው ገቢ እና በበጎ አድራጊዎች ታግዞ ጎጆ ቤትዋ በመሰራት ላይ ትገኛለች እንግዲህ በሰማዕቷ መልካም ፈቃድ በቀን 28/05/09 ዓም ጸሎተ ምህላ አድርሰን ቅዳሴ ቤቷን ለማክበር በዝግጅት ላይ እንገኛለን የሰማዕቷ ወዳጅ የሆነ ሁሉ በቤቷ እንድትገኙ ጥሪዋን ታስተላልፋለች ፡፡ታዋቂው እና ፈዋሹ የሰማዕቷ የማር ጸበል እንዳያመልጣችሁ ይህም ከመቅደሳ የተገኘ ነው ፡፡እንዲሁም ሀብተ ፈውስ ባላቸው አባት በመምህር አብርሃም የጸበል አገልግሎት ይሰጣል ፡፡ አድራሻ ከጎሮ ወደ ቱሉዲምቱ በሚወስደው መንገድ ላይ ሁለተኛውንና ትልቁን ድልድይ ሳይሻገሩ አስፋልቱ ዳር ላይ ይገኛል እግዚአብሔር አብ እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ፡፡ለበለጠ መረጃ 0913511802 ወይም 0936451511ይደውሉ፡፡ በተጨማሪ ☞መንፈሳዊ ጉዞ የምታዘጋጁ መንፈሳዊ ማህበራት አና የቤተክርስቲያን ልጆች ወር በገባ በ 6 ወደዚህች የበረከት ደብር በሆነች ምዕመናንን እንድታስጎበኙልን እና ምዕመናንን የበረከቱ ተካፋይ ታደርጓቸው ዘንድ ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች ቤተክርስቲያናም ማንኛውንም መንፈሳዊ ተግባራት ታከናውናለች ፡፡የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ በረከት ይደርብን አሜን፡፡
ጸሐፊ ዲ/ን ኤርምያስ ግርማ


የቅድስት አርሴማ አዲስ ፀበል


Wednesday, January 4, 2017

የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፀበል

ይህ የምታዩት የተአምረኛው የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፀበል ነው። ይህ ፀበል ብዙ ድውያንን ከተለያዩ ሀገራት ዝናውን ታሪኩን በመስማት እየመጡ ከበሽታቸው ፀበሉን በመጠመቅ፣በመጠጣት ብዛት ያላቸው ሰወች ከስቃያቸው ተፈውሰዋል።

ፀበሉ የሚገኝበት አካባቢ በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን  በቋራ ወረዳ በበርሚል ቀበሌ ይገኛል። ሽር በማድረግ በሰማዕቱ ስም ይተባበሩን የሰማዕቱ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።