Tuesday, November 10, 2015

የ ኪዳነ ምሕረት ተአምር

የሚገርም የእመቤታችን ማርያም ተአምር ታሪክ ፦በራያ አልማጣ በጥሙጋ ከተማ ኪዳነ ምሕረት በተባለች ቤተክርስቲያን ለበተክርስቲያኑ ግንባታ የሚሆን ድንጋይ በመኪና ተጭኖ ከመጡት ብዙ ድንጋይ መካከል አንደኛው ድንጋይ ሲጠረብ አልጠረብም ይላል አሁንም ግንበኞቹ በተደጋጋሚ ሞከሩ ሊጠረብ አልቻለም ከዛ ሳይጠረብ ለግንባታ ሊጠቀሙበት ወደ ላይ ለመስቀል አንደኛው ግንበኛ በሁለት እጁ ተሸክሞ ወደ ላይ በሚወጣበት ጊዜ የተሸክመው ሰው እዛው ባለበት ቦታ ልክ እንደ ኤሌክትሪክ ይነዝረዋል ከዛም ከላይ ወደታች ሲወድቅበት ያ ተአምረኛ ድንጋይ ከ ሁለት ይከፈላል በጣም በሚገርም ሁኔታ ከአንደኛው ድንጋይ የምትመለከቱት የእመቤታችን ሥዕል ታየ በጣም የሚገርመው ለ 3 ዓመት መራመድ ያቃታት ሴት የድንጋዩ ፍንጣሪ እግሯን ሲመታትፈውስ አገኘች ማየት ማመን ነው ጥሙጋ እየመጣቹህ መመልከት ትችላላቹህ የእመቤታችን አማላጅነት አይለየን አሜን

No comments:

Post a Comment