Tuesday, September 30, 2014

በልበሌቲ ጽጌ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን

በልበሌቲ ጽጌ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከአዲስ አበባ 418 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ቦታውም ለመድረስ ከአዲስ አበባ በናዝሬት፣ አሰበ ከዛም በበዴይሳ አድርገው ወደ ገለምሶ ይጓዛሉ በመጨረሻም ቤተክርስቲያኑ የሚገኝበት በልበሌቲ መሻገር ይኖርቦታል። መንገዱ ለማንኛውም መኪና ምቹና ቤተ ክርስቲያኑም መንገድ ዳር በመሆኑ ምንም እንግልትና የእግር ጉዞ የለውም።

ይህ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው በምዕራብ ሐረርጌ ሐብሮ ወረዳ በልዩ ስሙ በልበሌቲ በመባል በሚታወቀው መንደር ሲሆን ለምዕራብ ሐረርጌ የመጀመሪያው ቤተክርስቲያን ነው። የተተከለውም በእምዬ ምንሊክ በፊታውራሪ ዘመንፈስ በ1870 ከአርሲ እያስገበሩ ሲመጡ በምዕራብ ሐረርጌ ሲያልፉ እንደተከሉት ይነገራል። ቤተ ክርስቲያኑ ሲዘዋወር አሁን ያለበት ቦታ ሰባተኛው ሲሆን እምዬ ምንሊክ ለቤተ ክርስቲያኑ የሰጡት ርስት 18 ጋሻ መሬት ቡሩሪ በሚባል ቦታ ህንጻውም ባለ ደርብ(under ground) የሆነ ነበር። በጣልያን ወረራ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ በመቃጠሉ ከተሰጠው ርስት በመነሳት በሽሽት ቀርጫ የሚባል ጫቃ ውስጥ ለ 5 ዓመት ስብሐተ እግዚአብሔር ሲደርስ ቆይቷል። በዚህ ወቅት ያ 18 ጋሻ መሬት የለውም እዛ ቦታ ላይ ሌሎች ሁለት ቤተ ክርስቲያን ታንጸው እሱ የሚገኘው ሌላ አዲስ በተመራው ቦታ ላይ ነው። በዚህ ቤተ ክርስቲያን የሚነግሱ ታቦታት ሶስት ሲሆኑ እነሱም ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚያዚያ 23ና ጥር 18፣ ኪዳነ ምህረት በየካቲት 16፣ ሩፋኤል በጷግሜ 3 ይነግሳሉ።

ደብሩን ምን ልዩ ያደርገዋል

ስለት ሰሚነቱ
በአገር ውስጥም ከአገር ውጪም ባሉ የአካባቢው ሰዎች የበልበሌቲው ጊዮርጊስ አንተው ስለቴን ፈጽምልኝ ብለው የተሳሉ ሁሉ ላመኑት ክርስቲያኖች ብቻ ሳይሆን ከክርስናው ውጪ ላሉትም ሰዎች እንኳ ሳይቀር ስለታቸው ደርሶላቸው በድብቅ (ሰው በመላክ) በግልጽም (ራሳቸው በመምጣት) ስለታቸውን ይልካሉ። በሐኪም እንደማይወልዱ የተነገራቸው፣ ትዳር ያጡ፣ በህመም የሚሰቃዩ፣ ውስብስብ ችግር የገጠማቸው፣ ብዙ ብር ጠፍቶባቸው የነበሩ ሌሎች ሌሎችም የህይወታቸው እንቆቅልሽ ተፈቶላቸው አምላከ

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?

የኢንተርኔት አገልግሎት ፈጣን ባልሆነበት ቦታ በአማራጭነት ይህንን በጽሑፍ መልክ ያንብቡ:: ረጅም ትምሕርት ሲሆን በተቻለ መጠን በቂ መልክቱን በጽሑፍ አቅርበናል:: የቃላት ግድፈት ካለ እያረሙ እንዲያነቡ እንጋብዛለን::
የጸሎት ቦታ እንዴት ላዘጋጅ?

ክፉንና ደጉን ለመለየት አምልኮ ያስፈልጋል:: አምልኮ የሌለበት ህይወት አለም ላይ የወደቀ ነው ስለዚህም የአምልኮት ራእይ አንድ ክርስቲያን ሊኖረው ይገባል:: ማምለክ ማለት እግዚያብሔርን ከልብ መውደድ: ቃሉን በልቦና ማኖር: እና መጠበቅ: እርሱን ተስፋ ጉልበታችንን ማድረግ ነው:: በተግባር ደግሞ ኑሮን ጠባይን ለእግዚያብሔር መስጠት: ውስጣዊ ህይወታችንን ለክብሩ የተዘጋጀ ማድረግ :: ስለ ሐጢአታችን ንሰሐ ገብተን ሥጋውና ደሙን መውሰድ: እለት እለት ስለበደላችን ስለሐጢአታችን ለእግዚያብሔር መንገር:: እለት እለት እግዚያብሔርን የምናመሰግንበትን ግዜ ካገኘን የአምልኮት ሕይወት ገበና አለን ማለት ነው:: ሰብአ ሰገል ክርስቶስን በፍቅር ፈልገው እንደመጡ አንድ ክርስቲያንም ክርስቶስን ፈልጎ መምጣት አለበት:: በአምልኮት ባሕርይ ሔሮድስን ማለፍ ቅድሚያ የሚሰጠው ነገር ነው:: ሔሮድስ ማለት የዚህ አለም ነገሮች ናቸው እነዚህም :የአለምን ሰዎች እውቀት: ሳይንስ እግዚያብርሔን የሚከለክል : የድንግል ማርያም ልጅ ክርስቶስን የሚከለክል ነው:: ሔሮድስ ማለት ሐብት : ስልጣን: ማዕረግ የመሳሰሉት እነዚህ ሁሉ የሔሮድስ መንገድ ጠቋሚ ናቸው:: ሰዎች የጥፋት ሞት ውስጥ የሚገቡት የአምልኮት ሕይወት በማጣት ነው:: እግዚያብሔርን የሚፈልጉ ሰዎች ሔሮድስ ጋር መቅረት የለባቸውም:: ኮከቡን ማየት አለባቸው ኮከቡም ያለው በሰማይ ነው::

ብዙ ክርቲያኖች ወደ እግዚያብሔር ቤት አይሔዱም ወይም ወደ ሰማይ ቀና አይሉም:: በዚህም ወደ ልባቸው የሚሔድባቸው መጣባቸው:: ሰይጣን ወደ ቤታቸው ወደ ኑሮአቸው ወደ ሕይወታቸው መጣ:: በዚህ ዓለም ገለልተኛ ሆኖ መኖር አይቻልም:: በዚህ አለም ሁለት ነገር ነው ያለው:: ጽድቅና ኩነኔ: ጨለማና ብርሃን: ሓጢአትና ጽድቅ: ሰላምና ጦርነት::ከፈለክ ወደ ብርሃን ካልፈለክ ወደ ጨላማ: ከፈለክ  እውነት ካልፈለክ ሐሰት: እንዲህ በጥንድ የተያያዘ ነው:: የእግዚያብሔርን በቅድምያ ከሰማን የእግዚያብሔር ጽድቅ ይገለጥልናል: የሰዎችን ከሰማን ሁል ግዜ እንደተደናገግርን ተስፋችንን በአልሆነ አቅጣጫ እየጠበቅን እንኖራለን:: ሔሮድስ ክፉ መሆኑን የምናውቀው ስናመልክ ነው::

የጸሎት ቦታ
የጸሎት አቅጣጫ ምስራቅን የተመለከተ መሆን አለበት:: በመንበርከክ በግንባር ልክ የእመቤታችን የቅዱስ ሚካኤል የቅዱስ እና የቅዱስ ገብርኤል በግራና ቀኝ : በመቆም ልክ የስላሴ የመድኃኔአለም ስእል ይደረጋል:: ከስእሉ ራቅ የሚባለው ክፍተቱ የመጽሐፍ መግለጫ ያህል ነው:: ስእሎቹ ተጸልዮባቸው ቅባ ቅዱስ ይቀባሉ ቢቻል ቤተ ክርስቶያን ተባርካው በቅዳሴ ግዜ ቅባ ቅዱስ ተቀብተው መሆን አለበት:: ስእሎቹ በጥሩ ፍሬም የተሰሩ ስእሎች መሆን አለባቸው:: ከስራቸው የጸሎት ወሃ : እጣን: እምነት:የወይራ ዘይት: የመጽሀፍ ማስቀመጫ: የምንጠቀምባቸው እንደ ሽቶ ዎች ካሉ አጠገብ መሆን አለባቸው:: ሽቶ የሚወዱ ዛሮች አሉ:: ተጸልዮበት ሽቶ ብንጠቀም ሽቶ የሚወዱ ዛሮችን መከላከል ይቻላል : የመንበርከኪያ ቦታ ደረቅ ያለ የጥጥ ፍራሽ ቢሆን ይመረጣል:: ግልበት በሚሰግድበት ግዜ መመቻቸት አለበት ነገር ግን በጣም የሚመች ሥፕንጅ መሆን የለበትም: ስንፍና እንዳይሰማው: የሚሞቅ ነገር መሆን የለበትም መቀዝቀዝም የለበትም:: በሚሰግድበት ግዜ በስእሎቹ ፊትለፊት  መስገድ ሲጀምር የሚከተሉትን ምልክቶች ያያል:- መዛል:መድከም መልፈስፈስ :: በሚጸልይበት ግዜ ከስእሎቹ የሚወጣ መንፈሳዊ እሳት አለ:: በሰውነቱ ላይ ከስእሎቹ ተጠግቶ ሲጸልይ መውረር መቅበጥበጥ:ማቃጠል የሚታይበት ይሆናል:: አንዳንዱም መንፈሱ ወዲያው መገለጥ ጠባይ አለው:: መንፈሱ ጸሎት በከፍተኛ ሁኔታ ጸሎት እየከለክለው የሚያጠቃው ከሆነ የቅዱስ ሚካኤልን ስእል በፍሬም በጥሩ ሁኔታ ሰርቶ  መሬቱ ላይ አድርጎ እጁ ላይ እና ሰይፉ ላይ በሚሰግድበት ግዜ መንፈሱ ሊጥለው ይችላል:: በዚህ ግዜ መቁጠርያ ያስፈልጋል::ጸጥ በል በጌታየ በየሱስ ክርስቶስ ስም ብሎ ሲመታው ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እሰርልኝ ሲለው  በስእሉ ፊት ያለው ሐይል እየተገለጠ ቅዱስ ሚካኤል ሊያስርለት ይችላል:: ሰውየው እየሰማም እያወቀም መንፈሱን ሊያስርለት ይችላል:: በዚህ ግዜ ፕሮግራም ይዞ ወድ  እኔ ደውሎ አንዳንድ መረጃ እንለዋወጣለን:: የሚደክም ከሆነ ይደክማል የሚሸኝም ከሆነ ይሸኛል:: ሆኖም ግን  እነዚህን ልምምዶች በቀላሉ የሚመጡ  አደሉም:: ሰውየው በጥሩ የበረከት መንፈሳዊ ህይወት ለማለፍ እራሱን ማዘጋጀት አለበት:: ጸሎትን እንደ ደስታ አምላክን እንደማማረርያ ጎዳና ሳይሆን "ሁል ግዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ:ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ::ገርነታችሁ ለሰው ሁሉ ይታወቅ::" እንዲል ገራገር መሆን አለበት:: "ጌታ ቅርብ ነው::በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ::" ፊልጵስዮስ 4:4-6

ራእይን ምሪቱን ለማግኘት ደግሞ የጸሎት ቦታችን ላይ ለባልና ሚስት የመኝታ ያህል መኖር አለበት: ቤተሰብ ካለው ከሌለው